ኢሕአዴግና በሽብርተኝነት የተፈረጁት 5 ድርጅቶች

እስክንድር ነጋ (አዲስ አበባ)

 

ዘንድሮ ዲሽ በየደሃው ቤት እንኳን ዘልቆ ገብቷል። ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን መደበቂያ መሆኑ ነው እንጂ፣ ብዙሃኑ ህዝብ እንግሊዝኛውንም ሆነ አረብኛውን አይሰማም። አበው፣ «የቸገረው እርጉዝ ያገባል» እንዲሉ፣ በኢቲቪ ከመጨቅጨቅ ከአረብ ሳት ምስሎች ጋር መፋጠጡን መርጧል። የሚባለው ለምናባዊ ጨዋታ (imaginative conversation) የሚተው ነው። አስቂኝም አሳዛኝም ነው። ህዝብ የሀገሩ ባለቤት ሳይሆን እንዲህ ነው። ትራጂ ኮሜዲ ይሉታል ፈረንጆች። እየሳቁ ማልቀስ ማለታቸው ነው። ይህን ይመስላል የኢትዮጵያዊያን ኑሮ፤ በዘመነ ኢሕአዴግ።