የፓርላማው አባላት ያጨበጨቡት ለምንድነው?

ታደሰ ብሩ

ይህንን ዜና ምን ትሉታላችሁ?

ዋናው ኦዲተር የፓርላማ አባላትን ያስጨበጨበ ሪፖርት አቀረበ

የፌዴራል ዋና ኦዲተር፣ ዛሬ ለተወካዮች ምክር ቤት ያቀረበው የፌዴራል መንግሥት መሥርያ ቤቶች የ2002 በጀት ዓመት ሒሳብ ኦዲት ሪፖርት የፓርላማ አባላትን አስጨበጨበ። በርካታ የመንግሥት መ/ቤቶች የአፈጻጸም ጉድለቶችን ፈጽመዋል። ሪፖርተር ጋዜጣ ሰኔ 1 ቀን 2003 ዓ.ም.

ለምንድነው የፓርላማ አባላቱ ያጨበጨቡት? የኦዲተሩ ሪፖርቱ ምን አስደናቂ ነገር ይዟል? ቀጥለን ያለውን አንቀጽ እናንብብ።