በየመን አመፅ ቁጥራቸው ያልታወቀ ኢትዮጵያውያን ሞተዋል

– ኢትዮጵያውያኑን ወደ አገራቸው የማስመለስ ሒደቱ ቀጥሏል

ከሦስት ወራት በፊት በየመን በተቀሰቀሰው ሕዝባዊ አመፅ ቁጥራቸው ያልታወቁ ኢትዮጵያውያን ዜጐች መሞታቸውን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና ዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት (አይኦኤም) ሰኔ 3 ቀን 2003 ዓ.ም. በሒልተን ሆቴል በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቁ፡፡