አንድ ሄክታር መሬት ከሃያ ብር ባነሰ
በኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው የመሬት ነጠቃ የተዘጋጀ ልዩ ጥናታዊ ዘገባ

Ethiopia Zare (ዓርብ ሰኔ 3 ቀን 2003 ዓ.ም. June 10, 2011)፦ አንድ ሄክታር መሬት በአንድ ዶላር ከ19 ሣንቲም (በኢትዮጵያ ከሃያ ብር ባነሰ ገንዘብ) በ”ኢንቨስትመንት” ስም ለ99 ዓመታት በሚቆይ ሊዝ የኢህአዴግ መንግሥት የኢትዮጵያን መሬት እየቸበቸበ፤ ህዝቡን ለዘመናት ከኖረበት ቀዬ እያፈናቀለ መሆኑን የኦክላንድ ተቋም እና የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ በቅንጅት ባካሄዱት የጥናት ዘገባ ገለፁ።