አርእስተ ሰበር ዜና:- የቅ/ሲኖዶስ 6ኛ ቀን ውሎ
(ደጀ ሰላም፤ ሜይ 23/2011):-
- ጌታቸው ዶኒ አላግባብ ከተሾመበት ሥልጣኑ ተወገደ፤ የሐዋሳ ደ/ም/ቅዱስ ገብርኤል ገዳም አስተዳዳሪም ተነሥተዋል፤ የሁለቱ አድባራት አስተዳዳሪዎችም በቀጣይ በሊቀ ጳጳሱ ውሳኔ እንደሚነሡ ይጠበቃል
- ‹‹ሹመቱ ከሕግ ውጭ ነው፤ ሕግ ተላልፈዋል፤ ሕግ መከበር አለበት፤ ቤተ ክርስቲያን በሕግ የምትመራ ናትና፤›› (ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ)
- ፓትርያሪኩ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የገዳማት እና አድባራት አስተዳዳሪዎችን፣ ጸሐፊዎችንና ጋዜጠኞችን በመጥራት ለመስጠት ያቀዱት መግለጫ በሲኖዶሱ አባላት ታገደ፤
- የመግለጫው ዋነኛ ዓላማ ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቤተ ክርስቲያኒቱን አስተዋፅኦ ለመግለጽ ነው ቢባልም የምልአተ ጉባኤው አባላት ባልወሰኑበት ሁኔታ ‹‹የሲኖዶሱን መጠናቀቅ በማስመልከት ነበር›› የሚሉ መረጃዎች እየወጡ ነው፡፡
- ምልአተ ጉባኤው ከቀትር በኋላ በሰንበት ት/ቤቶች እና በማኅበረ ቅዱሳን መካከል ባለው ችግር ላይ መነጋገሩን ቀጥሏል::