ስምዐ ጽድቅ ታተመች


(ደጀ ሰላም፤ ጁን 7/2011)፦ ከሥርዓት ውጪ በተደረገ ደብዳቤ እና የስልክ ልውውጥ ሕትመቷ ተስተጓጉሎ የነበረው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ጋዜጣ ስምዐ ጽድቅ በዛሬው ዕለት በሌላ ማተሚያ ቤት ታት መሠራጨ ጀምራለች። ከ1985 ዓ.ም ጀምሮ በመታተም በሕትመት ብዛት እና ረዥም ዓመታት በማሳለፍ ቀዳሚ የሆነው ይህ ጋዜጣ ለብዙ ጊዜያት ያለመታተም እንቅፋት ቢገጥማትም እንደ አሁኑ ከፍ ያለ ፈተና እንዳልደረሰት ምንጮች አስረድተዋል። ብዙዎች ምዕመናን “መምህራችን” የሚት ጋዜጣ መቋረ በደጀ ሰላም ከተዘገበበት ጊዜ ጀምሮ ከፍተኛ ቁጣ መቀስቀሱን የተረዳን ሲሆን ቤተ ክህነቱ አሁን በያዘው መልኩ የሚሔድ ከሆነ ምዕመናን የራሳቸውን መፍትሔ ወደ መፈለግ እና በደብረ አሚን አቡነ ተ/ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን እንደታየው ዓይነት “ጉልበት ወደ መጠቀም” የመሰለ አላስፈላጊ መፍትሔ እንዳይዘዋወሩ አስግቷል።