የአፍሪቃ ቀንድ አለመረጋጋትና የስደተኞች ይዞታ

ለስደቱ እየተባባሰ መሄድ፣ በሃገራቱ የተለያዩ መንስኤዎች መኖራቸው ቢታወቅም በጥቅሉ ግን ፖለቲካዊ ኤኮኖሚያዊ ችግሮች በዋነኛ በምክንያትነት ይጠቀሳሉ። ዜጎቻቸው ለስደት የሚዳረጉባቸው እነዚህ ሃገራት ደግሞ በርካታ የየጎረቤት ሃገራት ስደተኞችን ተቀብለውም ያስተናግዳሉ።