የኦባማ የአፍሪቃ ጉብኝት ፍፃሜ

የዩኤስ አሜሪካ ፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ ትናንት በሴኔጋል፣ በደቡብ አፍሪቃ እና በታንዛንያ ያካሄዱትን የአንድ ሣምንት ጉብኝታቸውን አጠናቀቁ። ኦባማ በጉብኝታቸው ወቅት በአህጉሩ ያለውን ግዙፍ የኤኮኖሚ ዕድል በማመልከት፣ ሀገራቸው በዚሁ ዘርፍ ከአፍሪቃ ጋ ግንኙነትዋን እንደምታስፋፋ አስታውቀዋል።