የመሬት ንጥቂያውና የወደፊቱ መከራችን

ሉሉ ከበደ (ካናዳ)

ቀደምት የሐገራችን አንባገነኖች ሕዝባችንን ሲገሉና ሲያስሩ ሲያሰቃዩ የነበረው  ባብዛኛው ስልጣናቸውን ለመጠበቅ ሲሉ መሆኑ ብዙም የሚያከራክረን አይደለም።  አሁን ያሉት ግን ለስልጣንም፤ ለገንዘብ፤ ለሐብትም ሖኗል። የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዳለፉት ሀያ ዓመታት መብቱ ተገፎ፤ ሰብእናው ተረግጦ፤ ተከፋፍሎ፤ ታስሮ፤ ተገሎ፤ ተዘርፎ፤ ለህይወቱና ለንብረቱ፤ ለስራው፤ ለኑሮው ዋስትና አጥቶ፣ ፈርቶ፤ ተጨንቆእንዲኖር የተደረገበት ዘመን ቢኖር አሁን ነው።