የሴ ካ ፋ ግጥሚያ እና ፖለቲካዊ መልዕክቱ

በእግሊዝኛ ምሕፃሩ ሴ ካ ፋ የሚባለዉ የእግር ኳስ ማሕበር የሚያስተናብራቸዉ 11 የምሥራቅ እና የማዕከላይ አፍሪቃ አገሮች የእግር ኳስ ቡድኖች በሱዳን የዳርፉር እና የደቡብ ኮርዶፋን ግዛቶች አመታዊ የዋንጫ ግጥሚያቸዉን ባለፈው ሣምንት ማክሰኞ፣ እአአ ሰኔ 18፣ 2013 ዓም ጀምረዋል።