የፕሬዝዳት ኦባማ ጉብኝትና ንግግር በበርሊን

ኦባማ በንግግራቸዉ የሰዉ ልጅ እኩልነት፥ የመንቀሳቀስና የመሥራት መብቱ እንዲከበር፥ የኩሌር ጦር መሳሪያ ቅነሳ እንዲደረግ ጠይቀዋል።አስተናጋጃቸዉ የጀርመንዋ መራሒተ መንግሥት ወይዘሮ አንጌላ ሜርክልም የዲሞክራሲ ሥርዓትና የሕዝብ ነፃነትን ማክበር አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል