የዐባይ ግድብ ፣ የኢትዮጵያ ፓርላማና ተቃዋሚዎች

የኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአባይ ተፋሰስ ሃገራትን የትብብር ስምምነት ዛሬ አፀደቀ ። በ547 ቱ የምክር ቤቱ አባላት በሙሉ ድምፅ የፀደቀው ይኽው ስምምነት የአባይ ወንዝ ውሐ ዋነኛ ተጠቃሚ ለሆኑት ለግብፅና ለሱዳን የላቀ መብት የሚሰጠውን የቀደመውን የቅኝ ግዛት ዘመን ውል የሚተካ አዲስ ስምምነት ነው ።