የአባይ ግድብ የግብፅ ተቃውሞና የኢትዮጵያ መልስ

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ ኢትዮጵያ ዓለም ዓቀፉ የግድቡ አጥኚዎች ቡድን ያቀረበውን የጥናት ውጤት እንደገና የመከለስም ሆነ የግድቡን ሥራ የማስቆም ሃሳብ እንደሌላት ለዶቼቬለ ተናግረዋል ።