የዚምባቡዌ ምርጫ ዝግጅት

ዚምባቡዌ ለምርጫ እየተዘጋጀች ነዉ። የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሞርጋን ቻንጊራይ አስቀድሞ አንዳንድ ማሻሻያዎች መደረግ እንደሚኖርባቸዉ እያሳሰቡ ነዉ። ፕሬዝደንት ሮበር ሙጋቤ በበኩላቸዉ ህገመንግስታዊዉ ፍርድ ቤት በወሰነዉ መሠረት ምርጫዉ በሐምሌ ወር ማለቂያ እንደሚካሄድ ይፋ አድርገዋል።