ህዝባዊ ተቃውሞ በቱርክ

በቱርክ ዐብይ ከተማና የንግድ ማዕከል በኢስታንቡል በመቶ ሽህ የሚቆጠሩ ተቃዋሚ ሰልፈኞች ጠቅላይ ሚኒስትር ረችብ ታይብ ኤርዶጋን ስልጣን እንዲለቁ ጠየቁ። ባለፈዉ ሳምንት መጠናቀቅያ ላይ በቱርክ የታየዉ የተቃዉሞ ሰልፍ ከአስር አመት ወዲህ የመጀመርያዉ እንደሆንም ተነግሮአል።