በዚህ ዓመት 12 ሺህ ደቡብ ሱዳናዊያን ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል መባሉን ዩኤንኤችሲአር አስተባበለ

በያዝነው የአውሮፓዊያን ዓመት ከደቡብ ሱዳን እየተሰደዱ ወደ አጎራባች ሃገሮች የገቡት ደቡብ ሱዳናዊያን ቁጥር ከ19 ሺህ እንደሚበልጥ የተለያዩ መገናኛ ብዙኃን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን እየጠቀሱ ቢዘግቡም የመንግሥታቱ ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር የኢትዮጵያ ቢሮ የተጠቀሰው ቁጥር ትክክል አለመሆኑን አስታውቋል፡፡

ዘገባውን የመንግሥታቱን ድርጅት ጠቅሰው ያሠራጩት ራዲዮ ባኺታ ኤፍ ኤም የሚባል የደቡብ ሱዳን ራዲዮ ጣቢያ፣ ሮይተርስ እና አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ ናቸው፡፡

በዚህ ዓመት ማለትም ባለፉት አምስት ወራት ብቻ ከደቡብ ሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የፈለሰው ስደተኛ 12 ሺህ እንደደርስና ከሚያዝያ 29 እስከ ግንቦት 16/2005 ዓ.ም ባሉት ሁለት ሣምንታት ተኩል ጊዜ ውስጥ አራት ሺህ ስደተኛ መግባቱን ዘገባዎቹ ጠቁመዋል፡፡

ስለሁኔታውና ስለዘገባዎቹም ለቪኦኤ መግለጫ …