ሶርያ እና የአውሮጳ ህብረት ውሳኔ

የአውሮጳ ህብረት አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚንስትሮች ትናንት በብራስልስ ባካሄዱት ምክክር ላይ ህብረቱ በሶርያ ላይ የጣለው የኤኮኖሚ ማዕቀብ እንዲቀጥል ተስማሙ። ይሁንና፣ ሚንስትሮቹ ህብረቱ በሶርያ ላይ ያሰረፈውን እና የፊታችን ቅዳሜ የሚያበቃውን የጦር መሣሪያ ማዕቀብ ማራዘም ሳይሳካላቸው ቀርቶዋል።