የአፍሪቃ ኅብረት በአፍሪቃውያን ዕይታ

የአፍሪቃ ኅብረት ከዛሬ፤ ቅዳሜ ግንቦት 17 ቀን 2005 ዓም አንስቶ እያከበረ የሚገኘውን የወርቅ ኢዮቤሊዩ በዓል በማስመልከት የተለያዩ የዶቸ ቬለ ሬዲዮ ጋዜጠኞች በተለያዩ የአፍሪቃ አገራት ውስጥ ነዋሪ የሆኑ ግለሰቦችን አነጋግረዋል። «የአፍሪቃ ኅብረት ለእርስዎ ምን ትርጉም አለው?» አብይ ጥያቄያችን ነበር።