የአፍሪቃ አንድነት የ50 ዓመት ጉዞ

ሰኞ ግንቦት 12 ቀን 2005 ዓ.ም. አምስት መዓልት ብቻ መቁጠር ይጠበቃል። ከእዚያም 50ኛ ዓመቱን ደፈነ ይባላል፤ የአፍሪቃ አንድነት። እጎአ 1963 ዓ ም፤ የቀን ቀመሩ በአጠቃላይ የጎርጎሮሳውያኑ ነው፤ ግንቦት 25። ነፃነቷን ከቅኝ ገዢዎች አስጠብቃ የቆየችው ኢትዮጵያ አፍሪቃውያን ወዳጆቿን እመዲናዋ ጠርታ ሽር ጉድ ይዛለች።