በአፍሪቃ ቀንድ የጋዜጠኞች ይዞታ

ሶማሊያ ዉስጥ በያዝነዉ የጎርጎሮሳዊ ዓመት 2013 ከባተ የተገደሉ ጋዜጠኞች ቁጥር አምስት ደርሷል። ለጋዜጠኞች መብት የሚሟገተዉ ድንበር የለሽ ዘጋቢዎች /RSF/ ሰሞኑን አንድ የሶማሊያ ራዲዮ ጋዜጠኛ መገደሉን በማዉገዝ፤ መቅዲሾ ዛሬም ለጋዜጠኞችም ሆነ ለኗሪዎቿ ፀጥታዋ የተረጋገጠነዉ ማለት እንደማይቻል አመልክቷል።