የጠ/ሚ ኃይለ ማርያም ጉብኝት በአዉሮጳ

አቶ ኃይለ ማርያም የጠቅላይ ሚንስትርነቱን ሥልጣን ከያዙ ወዲሕ ለመጀሪያ ጊዜ በአዉሮጳ በሚያደርጉት ጉብኝት ነገ ብራስልስ-ቤልጅግ ዉስጥ ከሌሎች የአዉሮጳ ሕብረት ባለሥልጣናት ጋር ለመነጋገርም ቀጠሮ አላቸዉ።በብራስልስ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ግን ሥለ ጉብኝቱ የሚያቀዉ እንደሌለ አንድ የኤምባሲዉ ባለሥልጣን አስታዉቀዋል