የአባይን ግድብ መገንባት እንችላለን!

ግርማ ካሣ

በአገር ውስጥም ሆነ ከአገር ውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን በሰፊው እያነጋገረ ያለው ጉዳይ ቢኖር በቅርቡ የኢሕአዴግ መንግሥት ይፋ ያደረገው የአባይ ግድብ ፕሮጀክት ነው። አቶ መለስ ዜናዊ ምንም እንኳን የውጭ አገር መንግሥታትና ድርጅቶች እርዳታቸውን ለመዘርጋት ፍቃደኛ ባይሆኑም፣ ሰማኒያ ሚሊዮን የሚሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ በራሱ ገንዘብ ግድቡን መስራት እንደሚችል፣ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።