የቦስተኑ የቦምብ አደጋና የፀጥታ ስጋት

ትናንት 27 ሺህ ሯጮች በተሳተፉበት ማራቶን በወንዶች ሌሊሳ ዴሲሳ በአንደኛነት በሴቶች ደግሞ መሠረት ኃይሉ በሁለተናነት አጠናቀዋል ። ኢትዮጵያዊው ጀግና በድል የክብር ሪቫኑን በጥሶ ካለፈ ከ ሁለት ሰዓትት በኋላ ከሰአት በኋላ ከቀኑ 8 ሰአት ከ 45 ላይ ከመጨረሻው የማሸነፊያ መሥመር በግራ በኩል ታላቅ ፍንዳታ ተሰማ ።