ኢትዮጵያዊ መልኮች በአሜሪካ – መልክአ ኢትዮጵያ – ፮
ጽዮን ግርማ
ምስክርን የማውቀው ኢትዮጵያ ነው፤ ዛሬ አገኘኹት። በእናቱ ጫንቃ ላይ የነበረው ያ ሁሉ አይበገሬነት ጠፍቶ በፋርመርስ ሥጋ ቤት አንገቱን ደፍቶ ሥጋ ቆራጭ ኾኗል። ምስክር የወጣበት የውስጠኛው ክፍል የገባው ሥጋ ተስተካክሎ እየተቆራረጠ ለገበያ የሚዘጋጅበትና የሥጋ ዘሮቹን ተከትለው የሚመጡትን ቆሻሻዎች ማጽዳት ነው። ምስክር በቆምንበት የተሻለ ኑሮ እየመራ ስለመኾኑ አጠር አጠር አድርጎ ነገረኝ፤ …