የአንድነት አመራር አባላት ስሞታ

በረሃብ አድማ ላይ የሚገኙትን አባላቶቻቸውን ለመጠየቅ ከፍተኛ የአመራር አባላቱ ወደ ማረሚያ ቤቱ ቢሄዱም የማረሚያ ቤቱ ሃላፊ ስለሌሉ መግባት አትችሉም ተብለው ሳይጠይቋቸው መመለሳቸውን የድርጅቱ የፖለቲካ ጉዳዮች ሃላፊ ፣ ለዶቼቬለ በሰጡት ቃለ ምልልስ አስታውቀዋል ።