የሁለቱ ሱዳኖች ሥምምነትና ገቢራዊነቱ

አሁን በተቃራኒዉ ፔልስ እንደሚለዉ፥ ሁለቱም ሐራራ ያናወዘዉ ሰዉ ምሱን እሲኪያገኝ እንደሚቅበዘበዘዉ የነዳጅ ምርቱ እሲከጀመር እየተጣደፉ ነዉ።በሱዳን የቀድሞዉ የዩናይትድ ስቴትስ ልዩ መልክተኛ አንድሪዉ ናትሲዮስ እንደሚሉት ሱዳኖች የነዳጅ ምርቱን ለመጀመር ቢጣደፉ አይበዛባቸዉም።ሁለቱም የዚያ «ጥቁር ፈሳሽ» ጥገኛ ናቸዉ።