የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ወቅታዊ ሁኔታ

ሚሼል ጆቶጅያ የሃገሪቱ ህገ መንግሥቱ መታገዱንና ፓርላማውና ካቢኔውምም መበተኑን ትናንት ማምሻውን አስታውቀዋል ። የቀድሞው ዲፕሎማት ጆቶጅያ ወደ ነፃ ተዓማኒና ግልፅ ምርጫዎች ይወስደናል ያሉት 3 አመት ያህል የሚወስደው የሽግግር ጊዜ በአስቸኳይ ጊዜ ህግ እንደሚመራም ከዋና ከተማይቱ ከባንግዊ ተናግረዋል ።