የኦባማ የመካከለኛው ምሥራቅ ጉብኝት

የዩኤስ አሜሪካ ፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ በመካከለኛው ምሥራቅ በሚያደርጉት የአራት ቀናት ጉብኝት ዛሬ ቴልአቪቭ ገቡ። በዚሁ ወቅት የእሥራኤል ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና መላው የመንግሥት ካቢኔ ለአሜሪካዊው ፕሬዚደንት አቀባበል አድርገዋል።