የርዕስ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ በዓለ ሢመት

ባለፈው ሣምንት የተመረጡት የአዲሱ የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ርዕስ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ በዓለ ሢመት ዛሬ በቫቲካን ተከናወነ። የአርጀንቲንያ ተወላጅ የሆኑትን የርዕስ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስን በዓለ ሢመት እጅግ ብዙ ሕዝብ፡ በርካታ የሀገር መሪዎችም በሮም ተከታትለውታል። ከሮማ ወኪላችን ተኽለእግዚ ገብረኢየሱስ በስልክ አነጋግሬዋለሁ።