የጀርመን ፕሬዚዳንት የኢትዮጵያ ጉብኝት

የኢትዮጵያ ሠብዓዊ መብት ኮሚቴና በጀርመንኛው «ፔን ሴንትሩም ዶይችላንድ» ተቋም የጀርመኑ ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ስለሠብዓዊ መብትና ስለመናገር ነፃነት መገደብ በይፋ እንዲናገሩ በደብዳቤ ጠየቁ። በጀርመን ምክር ቤት የአረንጓዴዎቹ ፓርቲ እንደራሴና በምክር ቤት የኢኮኖሚ ትብብር ኮሚቴ ም/ሊቀመንበርም ተመሳሳይ ነጥብ አንስተዋል።