የኬንያ ምርጫ ዉጤትና አስተያየት

በኬንያ ባለፈዉ ሳምንት ሰኞ የተካሄደዉ አጠቃላይ ምርጫ ዉጤት ይፋ መሆን እስካሁን ያስከተለዉ ችግር የለም። የዛሬ አምስት ዓመት ምርጫ በከፍተኛ አመፅ መታጀቡ፤ ያም ያስከተለዉ የህይወት ጥፋትና የሰዎች መፈናቀል ቢያንስ ዛሬ እንዲደገም የሚፈልግ ወገን አለመኖሩ ሂደቱን በቅርበት የሚከታተለዉን ዓለም ዓቀፍ ኅብረተሰብ ከስጋት አሳርፏል።