ኢትዮጵያዊቷ ይሁዲ የቁንጅና ውድድር አሸናፊ

ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያዊቷ ይሁዲ የዘንድሮው የእስራኤል የቁንጅና ውድድር አሸናፊ ሆና ተመርጣለች። ቀድሞ የእስራኤል ጦር ውስጥ በውትድርና ታገለግል የነበረችው የቁንጅና ውድድሩ አሸናፊዋ ወጣት የሠራዊቱ አባል ሳለች ወቅት በሠራዊቱ ውስጥ እኩልነት እንዲሰፍን አጥብቃ የምትታገል እንደነበረችም ተገልጿል።