አጠቃላይ ምርጫ በኬንያ

በኬንያ አጠቃላይ ምርጫ በዛሬው ዕለት የተካሄደ ሲሆን፤ ቢያንስ 15 ሰዎች መገደላቸውን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። ከአምስት ዓመታት ቀደም ብሎ በኬንያ ተካሄዶ የነበረውን የምርጫ ውጤት ተከትሎ በተቀሰቀሰ ሁከት ከ1 ሺህ በላይ ሰዎች መገደላቸው የሚታወስ ነው።