የምርጫ ክርክር በኬንያ

የፊታችን ሰኞ ኬንያ ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ታካሂዳለች። ለዚህ ዝግጅትም በሀገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ፕሬዝደንታዊ እጩዎችን በምርጫ ክርክር ፊት ለፊት አሟግታለች። ከሁለት ሳምንታት በፊት የመጀመሪያዉ ዙር ሰኞ ምሽት ደግሞ የመጨረሻዉ እና ሁለተኛዉ ክርክር ተካሂዷል።