የኢትዮጵያ ብሔራዊ የሽግግር ምክር ቤት 2ኛ ጉባኤ አሜሪካን ውስጥ ተካሄደ (ጀርመን ራዲዮ)
የኢትዮጵያ ብሔራዊ የሽግግር ምክር ቤት 2ኛ ጉባኤ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ቨርጂኒያ አሜሪካን ውስጥ ተካሄደ። ጉባኤው የምክር ቤቱን የእስካሁኑ እንቅስቃሴ መገምገሙንና የወደፊት አቅጣጫውንም ማስተዋወቁን የዋሽንግተን ዲሲው ወኪላችን ዘግቧል ። በሌላ በኩል በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢዋ በሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያን አሜሪካውያን ሙስሊሞች አስተባባሪነት ባለፈው ቅዳሜ ዋይት ሃውስ ፊት ለፊት ሠላማዊ ሰልፍ ተካሄዷል። ስለ ቨርጂኒያው ጉባኤ ና ስለ ዋሽንግተን ዲሲው ሠላማዊ ሠልፍ አበበ ፈለቀ ዝርዝር ዘገባ አለው።