የሣምንቱ ስፖርት

ያለፈው ሰንበት የኢትዮጵያ አትሌቶች በተለያዩ ዓለምአቀፍ የማራቶን ሩጫ ውድድሮች ግሩም ውጤት ያስመዘገቡበት ነበር። በቶኮዮ ማራቶን ምንም እንኳ በወንዶች ድሉ የኬንያ ቢሆንም በሴቶች የኢትዮጵያ አትሌቶች የማይበገሩ ሆነው ታይተዋል።