የግራዚያኒ መታሰቢያና ተቃዉሞዉ

በሃያ-አምስት ከተሞች የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ተቃዉሟቸዉን በያሉበት አሰምተዋል።በየከተሞቹ የተሰበሰቡት ወይም አደባባይ የወጡት ኢትዮጵዉያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች የኢጣሊያ መንግሥትና የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን ለፋሽስቱ የጦር መሪ መታሰቢያ መቆሙን እንዲቃወሙ አቤት ብለዋልም።