የሰሜን አፍሪቃ ስደተኞች እና አውሮጳ

በጣሊያንና በአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት መሀል ስደተኞችን በተመለከተ ውዝግቡ ተካሯል። ጣሊያን ስደተኞቹን ተካፈሉኝ ብትልም ከህብረቱ ሀገራት በኩል የተሰጣት ምላሽ እዚያው እያሉ እናግዝሻለን እንጂ ወደ ሌሎች ሀገራት ስደተኞችን መላክ ተቀባይነት የለውም የሚል ነው።