በጅሃዳዊ ሐረካታ ፊልም ላይ ከ33ቱ ፔቲሽን ፈራሚዎች የተሰጠ መግለጫ

Ethiopia Zare (ሐሙስ የካቲት 7 ቀን 2005 ዓ.ም. February 14, 2013)፦ የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን በተከታታይ ያሳየውን ”ጅሃዳዊ ሐረካት” የተሰኘ ፊልም አስመልክቶ፤ ሰላሳ ሦስቱ ፔቲሽን ፈራሚዎች ባወጡት መግለጫ ”ለዘመናት በፍቅርና መከባበር የኖረን ህዝብ በደረቅ ፕሮፓጋንዳ መነጣጠልና መከፋፈልም ሆነ የመብት ጥያቄውን ማዳፈን አይቻልም!” በማለት በፊልሙ ላይ ያላቸውን ተቃውሞ ገልጸዋል።