በስዊድን 136 000 ክሮነር ለኢሳት ተሰበሰበ

አርቲስትና አክቲቪስት ታማኝ በየነ Artist and activist Tamagne Beyene on ESAT fundrising in Stockholm, Feb 10, 2013የገንዘቡ መጠን በስዊድን ከክብረወሰን ተመዝግቧል

ሙስሊሙና ክርስቲያኑ አንድነቱን ከመቼውም ጊዜ በላይ አሳይቷል

Ethiopia Zare (ሰኞ የካቲት 4 ቀን 2005 ዓ.ም. February 11, 2013)፦ ቅዳሜ የካቲት 2 ቀን 2005 ዓ.ም. በስዊድን ዋና ከተማ በስቶክሆልም በተካሄደው የኢሳት (የኢትዮጵያ ሳተላይ ቴሌቭዥን) የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት 136 ሺህ የስዊድን ክሮነር የተሰበሰበ ሲሆን፤ በዚህ ዝግጅት ላይ ሙስሊም ኢትዮጵያውን ከመቼውም ጊዜ በላይ ተሳትፎ ያደረጉበት መሆኑ ታውቋል።