የዳያስፖራው ፖለቲካ ቆሽሿል – ተሃድሶ ይስፈልጋ

አማኑኤል ዘሰላም

“ESAT is tasked to produce accurate and balanced news and information” ይላል የኢሳት ኤዲቶሪያል ፖሊሲ። ኢሳትን የሚያዳምጠው ሰው ጥቂት እንደማይሆን አስባለሁ። እስቲ በኢሳት የሚተላለፉ ፕሮግራሞችን እንመዝናቸው። ምን ያህል ሚዛናዊ፣ በእውነት ላይ የተመሰረተ፣ የሁሉን ወገኖች አስተያየት ያንጸባረቀ ዜናና ትንታኔ ይቀርባል? ምን ያህል በአገራችን ኢትዮጵያ መቀራረብ፣ ፍቅር፣ አንድነት እንዲሰፍን ይረዳል?