ማሊ፣ የለጋሽ ሀገራት ጉባዔ በአዲስ አበባ

የማሊ አማፂያንን ለሚወጋዉ ጦርና በጦርነቱ ለምትወድመዉ ማሊ ዳግም ግንባታ ገንዘብ ለማዋጣት ዛሬ አዲስ አበባ የተሰየመዉ ዓለም አቀፍ ጉባኤ ከአራት መቶ ሐምሳ ሚሊዮን ዶላር በላይ ለማዋጣት ቃል ገባ።የአፍሪቃ ሕብረት የሠላምና የፀጥታ ምክር ቤት ኮሚሽነር አምባሳደር ራምታ ላማምራ እንዳስታወቁት የተዋጣዉ የገንዘብ መጠን ከተጠበቀዉ በላይ ነዉ።