ይድረስ ለኢንተርኔት ድረ-ገጽ ኃላፊዎች

ከብዕር ስም ጀርባ

ብስራት ኢብሳ (ሆላንድ)

ድሮ የምደግፈው የነአበበ ጉርሙ የመቻል እግር ኳስ ቡድን ከጠፋ ከዓመታት በኋላ በትላንቱ ምሽት ለመጀመርያ ጊዜ የተከታተልኩትን፣ በደቡብ አፍሪካ፣ ብሔራዊ ቡድናችን ባሳዛኝ ሁኔታ በቡርኪና ፋሶ ተሸንፎ ጨዋታው ሲያልቅ፣ ተደብሬ የቴሌቭዥኑን መስመር ከኢሮ-ስፖርት ወደ ደች የዜና መስመር ቀይሬ ከባለቤቴ ጋር የዓለም ዜና ማዳመጥ ጀመርን።