ስለሂዩማን ራይትስ ዋች ክሥና ስለኤርትራ ሰብዓዊ መብቶች ከአምባሣደር ግርማ አስመሮም ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ

የሂዩማን ራይትስ ዋች ሪፖርት ተቀድዶ መጣል ያለበት ሠነድ ነው ሲሉ በአፍሪካ ሕብረትና በመንግሥታቱ ድርጅት የአፍሪካ የኢኮኖሚ ኮሚሽን የኤርትራ አምባሣደር ግርማ አስመሮም ከቪኦኤ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ተናግረዋል፡፡