የኦጋዴን ችግርና የቀድሞዉ የአካባቢዉ ወጣቶች መሪ

እስከተሰደደበት ድረስ የኖረበትን፥የኦጋዴንን ችግር-ለማቃለል ብልሐቱ ሁለት ነዉ-ባይ ነዉ-አብዱላሒ።በወጣትነት እድሜዉ «በቂ» የሚባል ሥልጣን፥ሥራዉን ምናልባትም ጥሩ ገቢ፥ ሐገር ኑሮዉን ትቶ ለመሰደዱ ምክንያት-የሚለዉ ብዙ ነዉ።ዋናዉ ግን በኦጋዴን ሕዝብ ላይ የሚደርሰዉ በደልና የሹማምንታቱ አሰልቺ «ዉሸት» ናቸዉ ይላል።