ለደን ጥበቃ የኅብረተሰብ ተሳትፎ

የኢትዮጵያ የደን ሽፋን ከጊዜ ወደጊዜ እየቀነሰ መሄዱ ተደጋግሞ የተገለፀ ጉዳይ ነዉ። በአንዳንድ አካባቢዎች ጭርሱን ተራቆቶ የነበረዉ ስፍራ በተለያዩ ስልቶች እንዲያገግም መደረጉ ቢነገርም ይህ ደን የሚባለዉንና የሀገሪቱን የተፈጥሮ ሀብት አይተካም የሚሉ ወገኖች አሉ።