በማሊ የአማጽያኑ ግስጋሴ ተገታ

የማሊ ጦር በፈረንሣይ አየር ሃይል በመረዳት ኮና የተሰኘችውን ሰሜናዊት ከተማ የአል-ቃኢዳ አበር ከሆነው እስላሚስት ቡድን ማስለቀቁን አስታወቀ። በዘመቻው አንድ የፈረንሣይ ጦር ሄሊኮፕተር አብራሪ ሞትዋል።