የተስፋይቱ ምድር ተስፋ እኛ “ወንድማማቾች ነን”

የተስፋይቱ ምድር ተስፋ እኛ “ወንድማማቾች ነን”

 ውድ ኢትዮጵያዊያንና ይሁዲ ወገኖቻችን

እኛ ኢትዮጵያዊ- እስራኤላዊያን ይሁዲዎች በሁሉም ዘርፍ ጠንክረን በብቃት ለመገኘትና በሁሉም አቅጣጫ ያለንን እምቅ ዕውቀትና ኃይል በማስተባበር በአንድነት በመቆም መብታችንን ከማስከበር አልፎ በማናቸውም በአገራችን በእራኤል ባሉ ከፍተኛ የሥራ አመራር መስኮች ላይ ለመሳተፍና ውጤት ለማምጣት በድርጅት መሰባሰብ ወሳኝና የማይታለፍ መሆኑንን ተገንዝበናል። በዚህም መሠረት እነሆ በተስፋይቱ ምድር ተስፋ የሚሆን ኢትዮጵያዊ- እስራኤላዊ ይሁዲዎችን መብት ለማስጠበቅ ብቁ ሆነን በመገኘት መሪ የመሆንን ተስፋ እግዚያብሔር ኃይል አድርገን እርሱ እግዚያብሔርም ያከናውንልናል ብለን በማመን በተስፋይቱ ምድር ተስፋ “እኛ ወንድማማች ነን” የሚለውን ፓርቱ በአገራችን በእስራኤል መስርተን ሌሎች መሰል የእስራኤል ፓርቲዎች ጋር ለመወዳደር እየተንቀሳቀስን መሆኑን እያበሰርን በመላው ዓለም የምትገኙ ወገኖቻችን ትብብርና ድጋፋችሁ እንዳይለየን እንጠይቃለን። ይህንን አስመልክቶ የወጣውን ሙሉ መግለጫ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ። ወንድማማቾች ነን