የሁለቱ ሐውልቶች ዕጣ 2

click here for pdf 
ዛሬ ጠዋት በተሰጠ መግለጫ የዐፄ ምኒሊክ ሐውልት አሁን ባለበት እንደሚቀጥል፡፡ የአቡነ ጴጥሮስ ሐውልት ግን ተነሥቶ ከግንባታው በኋላ እንደሚመለስ ተነግሯል፡፡ ዘግይቶም ቢሆን መግለጫው መሰጠቱ መልካም ነው፡፡ ነገር ግን አሁንም ዝርዝር የሚፈልጉ ነገሮች አሉ፡፡
  • የአቡነ ጴጥሮስ ሐውልት ተነሥቶ የት ነው የሚቀመጠው?
  • ማን ነው የሚያነሣው?
  • የቅርስ ባለሞያዎች ተሳትፎ ምን ያህል ነው?
  • በቆይታው ጊዜ የሚደረግለት ጥንቃቄስ?
  • ሲመለስስ የት ነው የሚቆመው? አሁን ከሚሠራው የባቡር መሥመር ጋር ባለው ተዛምዶ የወደፊት አቋቋሙ ምን ይመስላል?
ለወደፊቱ እንደዚህ ዓይነት ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ አስቀድሞ ዝርዝርናሉ መረጃ መስጠት ሊለመድ ይገባል፡፡