“የኢትዮጵያና የሕዝቧ ደመኛ …” ይሰቀል!

ብ/ጄኔራል መንግሥቱ ነዋይ (ግራ)፣ ገርማሜ ነዋይ (ቀኝ) Mengistu and Germame Newayሰሎሞን ተሰማ ጂ.

በ1900 ዓ.ም. በኢትዮጵያና በፈረንሳይ መንግሥታት ስምምነት፣ “በልዩ የቆመ ፍርድ ቤት” የሚል ስያሜ የተቋቋመ ፍርድ ቤት ነበር። ፍርድ ቤቱ የመጀመሪያ ሥራውን በ1914 ዓ.ም. ሲጀምር፣ የመጀመሪያው የፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት ብላቴን ጌታ ሕሩይ ወልደ ሥላሴ ነበሩ። ከርሳቸውም ቀጥለው የተሾሙትም ነጋድራስ አፈወርቅ ገብረየሱስ ናቸው። የዚህ ፍርድ ቤት ዋነኛው ተግባር የውጭ ዜጎች እርስ-በራሳቸው ሲጋጩና/ወይም የውጭ አገር ዜጎችና ኢትዮጵያውያን በተጋጩ ወይም በተካሰሱ ጊዜ ፍርድ መስጠት ነበር።